የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ደረጃን በተመለከተ ምልከታ ተደረገ፡፡

 
ጥር 29 ቀን 2017 ዓ/ም

የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሠጣጥ ጥራት ደረጃ ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ የባለስልጣን መ/ቤቱ የኤሌክትክ አገልግሎት ደንበኞች ዴስክ ቡድን የሰሜን አዲስ አበባ ሪጂን እና በስሩ ባሉ ሶስት ማዕከላት ላይ ምልከታ አደረገ፡፡ የምልከታ ቡድኑ በዋነኝነት በሪጂኑ ስር የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የአገልግሎት አሠጣጥ ደረጃና በደንበኞች እርካታ ላይ ትኩረት ያደረገ ምልከታ አድርጓል፡፡

በጉብኝቱ ወቅትም የአገልግሎት አሠጣጥ ስታንዳርዶች ስለመሟላታቸው እና በደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አቀባበልና አፈታት ስርዓት መኖርና መተግበራቸውን በተመለከተ ከሪጂኑ ዳይሬክተር እና ከማዕከሉ ኃላፊዎች ጋር ሠፊ ውይይትና የማዕከላት ጉብኝትየተደረገ ሲሆን በተጨማሪም ለአገልግሎት ተጠቃሚዎች አገልግሎት አሰሰጣጡን የተመለከተ መጠይቅ ተደርጓል፡፡

በባለስልጣን መ/ቤቱ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች ዴስክ ኃላፊ መቅደስ ይሄነው የምልከታውን ዓላማ አስመልክቶ እንደተናገሩት ባለስልጣን መ/ቤቱ በተሰጠው ተልዕኮ መሠረት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለህዝብ በማድረስ ሂደት የመንግሥት ማህበራዊ ፍላጎት የሟሟላት ዓላማ፣ የዘርፉ አልሚዎች ፍትሃዊ ተጠቃሚ የመሆን ፣ አገልግሎት ተጠቃሚው ህብረተሰብ ደግሞ ጥራትና ብቃቱ የተጠበቀ አገልግሎት የማግኘት በሶስት ወገኞች መካከል የሚኖርን ፍላጎት ማጣጣም ወይም ሚዛናዊ እንዲሆን ለማድረግ ተቋሙ የተጣለበትን ሃላፊነት ለመወጣት ነው ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ሰሜን ሪጂን ዳይሬክተር አቶ ይሄይስ ስዩም ለምልከታ ቡድኑ በሪጂኑ ስር በሚገኙ ማዕከላት የሚሰጡ አገልግሎቶች ጥራት ደረጃን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ በሪጂኑ በሚገኙ ሁሉም ማዕከላት ኤሌክትሪክን በአንድ ቀን በሚል የተቋሙ ንቅናቄ መሠረት አዲስ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ማገናኘትን በተመለከተ ደንበኛው የሚፈለግበትን መስፈርቶች አሟልቶ ከተገኘ ያለምንም ወረፋ በአንድ ቀን ኤሌክትሪክ እያገናኙ እንደሆነ፤ የደንበኞች ቅሬታ አቀባበል እና አፈታት ሥርዓትን በተመለከተ የደንበኞች ቅሬታ ተመዝግቦ በስታንዳርዱ መሠረት ለቅሬታቸው መልስ እንደሚሰጥና ከአቅም በላይ የሆኑ ችግሮች ሲያጋጥሙ ከነሱ በላይ ላለው መዋቅር ተልኮ መፍትሄ እንደሚሰጠው ተናግረዋል፡፡

በሪጂኑ አገልግሎት መስጫ ቁጥር 2 እና 4 ማዕከላት እንዲሁም በቁጥር 4 መዕከል በሚገኝበት ወረዳ የአገልግሎቱ ደንበኞች በሰጡት አስተያየት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተገናኘ መሻሻሎች መኖራቸውን፣ በማዕከሉ የቅድመ ክፍያ ካርድ ለመሙላት ፈጣን በመሆኑ በአዲስ አበባ ዙሪያ ቡራዩ አከባቢ ያሉ ነዋሪዎች ካርድ ለመሙላት በአቅራቢያቸው ያሉ ማዕከላት ወረፋ ሰለሚበዛቸው ወደነዚህ ማዕከላት በመምጣት እንደሚሞሉ አዎንታዊ ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን በአሉታ ከተነሱት መካከል የ905 የስልክ ጥሪ በፍጥነት ያለመነሳት እና የታቀዱ የጥገና ስራዎች ሲሰሩ በተቋሙ ስለሚሰጠውም ቅድመ ማስጠንቀቂያ ተደራሽ እንዳልሆኑ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ የምልከታ ቡድኑ ከሪጅኑ፣ከማዕከላቱ እና ከአገልግሎት ተጠቃሚ አካላት የተገኙ መረጃዎች ግብዓት የሚሰጡ በመሆናቸው ለቀጣይ ስራዎች አቅጣጫ የሚሰጡ እንደሚሆኑና በቀጣይም መሰል ስራዎች በሌሎች ሪጂኖች እና ክልሎች የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል፡፡

 

 

  • Hits: 1447

Contact Us

Petroleum and Energy Authority 

P.O.BOX 2554

Tel +251 

FAX +251

Email pea.info@pea.gov.et

Addis Ababa

Ethiopia

Address

Addis Ababa Kadco Group building #2 From 7th to 8th floor. Ethio china Friendship Avenue around Wello sefere.