የኢነርጂ መጠቀሚያ ዕቃዎች የጥራት እና የኢነርጂ ብቃት ደረጃ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡

 

ጥር 23/2017 (ነ.ኢ.ባ)

አነስተኛ ኢነርጂ ብቃት ደረጃ (MEPS) ለወጣላቸው ከውጭ ሀገራት ለሚገቡ የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎች የቅድመ ጭነት የጥራት ቁጥጥር ስርዓት (pre-export verification of conformity) የተመለከተ ስልጠና የቁጥጥር ስራውን ለሚሠሩ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባለሙያወች ተሰጠ፡፡

በባለስልጣን መ/ቤቱ የተዘጋጀው ይህ ስልጠና ብሔራዊ ኢነርጅ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂን ለማሳካት በተቀረጹ ፕሮግራሞች አንዱ በሆነው የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎች ኢነርጂ ብቃት ማሻሻያ ዓላማን ተፈፃሚ ለማድረግ ኢነርጂ አባካኝ ተብለው በተለዩ ከውጭ ሀገራት የሚገቡ የኤሌክትሪክ ሞተር፣ ማቀዝቃዣ ማሺኖች፣ጄኔሬተሮች፤ማከፋፈያዎችና ሶኬቶች ወደ ሀገር ውስጥ ከመግባታቸው አስቀድሞ ቁጥጥር ለማድረግ የሚያስችል የምርቶች ዝቅተኛ ኢነርጂ ብቃት ደረጃ የተመለከተ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይርክተረ አቶ ዲባራ ፉፋ ስልጠናውን በተመለከተ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአገራችን የሀይል አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ጠቁመው ለኢነርጂ ክፍለ -ኢኮኖሚ የሚሆን በቂ የኢነርጂ ፍጆታና ፍታሀዊ ተጠቃሚነት እንዲኖር ለማድረግ መንግስት የኢነርጂ አጠቃቀም ቁጥጥር እና ድጋፍ በመዘርጋት ለሁሉም በሁሉም ኢነርጂ ተጠቃሚ ዘርፎች በተለይም ለኢንዱስትሪዎች ሚፈልጉትን የሀይል መጠን ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በንግድና ቀጣናዊ ትስር ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ይርሳው ዘውዴ የስልጠናውን አስፈላጊነት አስመልክቶ እንደገለጹት በሀገር ውሰጥ የሚመረቱ፤ወደ ሀገር ውሰጥ የሚገቡ እና ወደ ውጪ ሀገር የሚላኩ የኢትዮጵያ ደረጃ የውጣላቸው ምርቶች ፤አገልግሎቶች እና ሂደቶች የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን በመቆጣጠር በሰዎች ፤በእሰሳት እና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ጥቅም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንያስከትል የኢትዮጵያ ደረጃዎች አዘገጃጅትና ማስተገበሪያ ሥርዓት ለመደንገግ በወጣው መሠረት አዋጅ ቁጥር 1343 /2016 አዋጁ ላይ እንደተደነገገ አስረድተው ይህንን ለማስፈፀም የቁጥጥር ስራዎች እየተሠሩ ነው ብለዋል፡፡
 
  • Hits: 1478

ኮንትሮባንድ እና ሕገ-ወጥ ንግድ የንግዱ ዘርፍ ዋነኛ ፈተናዎች በመሆናቸው በቅንጅት መታገል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ

 
የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ/ም
 
በቡታጅራ ከተማ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የንግድ ጉባኤ ከቀትር በፊት በነበረው ቆይታ የክልል ንግድ ቢሮዎች ፣ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር እና ተጠሪ ተቋማት ስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ከቀትር በኋላ በቀጠለው ጉባኤ በሪፖርቱ ግምገማ ወጤት የንግድ ዘርፉ ዋነኛ ማነቆ ሕገ-ወጥ አሰራር ነው በጋራ ልንታገለው ይገባል ተብሏል ። የንግድ ዘርፉ ለዘመናት አንቀውት የኖሩ ችግሮችን በአሰራር ማሻሻያዎች ለመቀየር የሚደረገው ጥረትን በዘርፉ ስር ሰደው የቆዩ የተሳሳቱ የንግድ እሳቤዎች በጤናማ የንግድ አውድ ውስጥ ተወዳድሮ ከመስራት ይልቅ ሕገ-ወጥነትን ምርጫ ያደረጉ በመሆናቸው የሚፈልገውን ውጤት ፍጥነት እንደሚገድቡ ተገልጿል ። በሕገወጥ ንግድ ከሚፈተኑ ዘርፎች አንዱ የነዳጅ ግብይት መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የፌድራል ተቋማት ከክልሎች ጋር በጋራ በመሆን ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት ጉባኤው ወስኖ መውጣት እንዳለበት አቅጣጫ ተሰጥቷል ።
 
  • Hits: 1648

የነዳጅ አከፋፋይ ኩባኒያዎች በስራቸው ከሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ጋር ውይይት በማድረግ ሪፖርት እንዲያቀርቡ አቅጣጫ ተሰጠ

 
ጥር 17 ቀን 2017 ዓ/ም

በነዳጅ ስርጭትና ግብይት ላይ በሚስተዋሉ ችግሮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት ከነዳጅ አከፋፋይ ኩባኒያዎች ጋር የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በዚሁ መድረክ ሚንስትሩ በሰጡት አቅጣጫ ሁሉም ኩባኒያዎች ከሶስት እስከ አምስት ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በስራቸው ከሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ጋር በችግሩ ዙሪያ ተወያይተው ሪፖርት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

በሚንስትሩ ለተሰጠው አቅጣጫ መነሻ የሆነ ሪፖርት የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሠሀርላ አብዱላሂ  በነዳጅ ስርጭትና ግብይት ላይ የሚፈጸሙ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ጥልቀትና ውስብስብነት በማሳረጃ የተደገፉ ማሳያዎችን ለኩባኒያዎች አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

በማሳያነት ከቀረቡት ችግሮች መካከል በአብዛኛው ከአዲስ አበባና ሸገር ከተማ ጨለማን ተገን በማድረግ በሕገ-ወጥ መንገድ ነዳጅ የመጫን እና የማዘዋወር ተግባር ስለመኖሩ፤ ነዳጅ የተጫነለትን መዳረሻ በመቀየር ወደ ኮንትሮቦንድ አከባቢዎች ማጓጓዝ፣ የነዳጅ መቅጃ ማሽኖች ላይ ወቅታዊ ጥገና ባለመደረጉ የትክክለኝነት ችግር መታየቱ፤ በወር መዳራሻ ሳምንታት የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ ይደረጋል በሚል እሳቤ ሠውሰራሽ እጥረት መፍጠር፤ ከነዳጅ ግብይት ስርዓት ውጪ የካሽ ግብይት ማካሄድ፤የሚሉት በዋነኝነት የቀረቡ ሲሆን እነዚህ ተግባራት ሲፈፀሙ ኩባኒያዎች ተገቢውን ክትትል ያለማድረግ፣ የነዳጅ ማደያዎች ያሉበትን ደረጃ ተከታትሎ ጥገና ያለማድረግ እና በማደያዎች መካከል ፍትሃዊ የነዳጅ አቅርቦት ሂደትን አለመከተል የሚሉት ተነስተዋል፡፡

በመንግስት መዋቅርም ውስጥ በየደረጃው የሚገኙ አካላት ተገቢውን ቁጥጥር ባለማድረጋቸው፤ሕገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን እይቶ በዝምታ ማለፍ እና ከማደያ በታች ለሚቀርቡ የችርቻሮ ፈቃድ ከሕግ አግባብ ውጪ ሕገ-ወጥ ደብዳቤ መፃፍ ነዳጅ በጀሪካን እንዲቀዳ መፍቀድ፤ ለችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄድ የራሳቸውን ኃላፊነት እንደሚወስዱ በቀረበው ሪፖርት ላይ ተመላክቷል፡፡

የቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ሃሳባቸውን የገለፁ የኩባኒያ ኃላፊዎች የተገለጹት ችግሮች መኖራቸውን እንደሚቀበሉ ገልጸው ዘርፉ ብዙ ተዋኒያን የሚሳተፉበት በመሆኑ ቅንጅታዊ አሰራርና መናበብ እንደሚያስፈልግ በተጨማሪም ዘርፉን እየፈተኑ ያሉ የሎጂስቲክ ማነቆዎች ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉ ሃሳባቸውን ሰንዝረዋል፡፡

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግና ሬጉላቶሪ ሚኒስትር ዲኤታ አብዱል ሀኪም ሙሉ (ዶ/ር) የጎላ የነዳጅ አቅርቦት ችግር በሌለበት የነዳጅ ዘርፉ እየተፈተነባቸው ያሉ ችግሮች ምንጭ ኮንትሮባንድና ሕገ-ወጥነት መሆኑን አፅኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ ችግሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ የመጣው የዘርፉ ተዋኒያን በአንድም በሌላም መልኩ ስለሚሳተፉበት ነው ያሉ ሲሆን ለዚህ ማሳያውም የነዳጅ አቅርቦት በኩባኒያዎች መርህ አልባ ግንኙነት በስራቸው ለሚገኙ ማደያዎች ፍትሃዊ አለመሆኑን በማሳያነት አንስተዋል፡፡

 

በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ በሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተሰጠ አቅጣጫ ሁሉም ኩባኒያዎች በእኩልነት የሚታዩበት አሰራር መኖሩን ገልፀው በነዳጅ ግብይት ላይ የሚታዩት ችግሮች በዋነኝነት አለአግባብ ለመበልፀግ ከሚመነጭ ገፍላጎት ስለመሆኑ የቀረቡው ሪፖርት ላይ የታዩ ማስረጃዎች ጠቋሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም በሕገ-ወጥነት ላይ እርምጃ ለመወሰድ ወደኋላ የማይባል መሆኑን በመረዳት ወደ አስገዳጅ እርምጃዎች ከመግባቱ አስቀድሞ ኩባኒያዎች በስራቸው ከሚገኙ ማደያዎች ጋር በመነጋገር ወደ-ሕጋዊ አሠራር እንዲመለሱ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ በመንግስት መዋቅር የሚገኙ አካላትን በተመለከተም ተመሳሳይ አቅጣጫ እንደተሰጠ ጨምረው ገልጸዋል::

 
  • Hits: 2075

ከመጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ

 
ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሰረት ስራ ላይ እንዲዉል በመንግስት ተወስኗል።
በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ:-
  • ቤንዚን በሊትር ----------------------ብር 112.67
  • ኬሮሲን በሊትር ----------------------ብር 107.93
  • ነጭ ናፍጣበሊትር --------------------ብር 107.93
  • ቀላል ጥቁር ናፍጣበሊትር --------------ብር 109.22
  • ከባድ ጥቁር ናፍጣበሊትር --------------ብር 106.75
  • የአውሮፕላን ነዳጅ 108.30 በሊትር -----ብር 11.3.20 መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
 

 

  • Hits: 2647

Page 1 of 6

Contact Us

Petroleum and Energy Authority 

P.O.BOX 2554

Tel +251 

FAX +251

Email pea.info@pea.gov.et

Addis Ababa

Ethiopia

Address

Addis Ababa Kadco Group building #2 From 7th to 8th floor. Ethio china Friendship Avenue around Wello sefere.