የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ቀጠና ሀገራት ኢነርጂ ተቆጣጣሪ አካላት ማህበር(RAERESA) ስብሰባውን በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

 
በምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ስር የሚገኘው የቀጠናው ሀገራት ኢነርጂ ተቆጣጣሪ አካላት ማህበር RAERESA የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ትስስርና ንግድ የሚመራበት የሕግ ማዕቀፍና ወጥነት ያለው የኤሌክትሪክ ታሪፍ ቁጥጥር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ከመስከረም 8-10 ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
 
በኮሜሳ የቀጠናው ሀገራት ኢነርጂ ተቆጣጣሪ ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሞሀሙዲኒ ኢሰኢፍ በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኮሜሳ በአባል ሀገራቱ መካከል የኢኮኖሚ ውህደት እንዲፈጠር እየሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኢኮኖሚ ውህደቱ አንድ አካል የሆነው በአባል ሀገራቱ መካከል የሚደረገው የኤሌክትሪክ ሃይል ንግድ የሚመራበትን ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የተጀመረው ፕሮጀክት በቀጠናው ሀገራት መካከል የሚገኘውን የሃይል አቅርቦት ትስስር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ተናግረዋል፡፡
ሞሀሙዲኒ እንደገለፁትም ፕሮጀክቱን ለመተግበር በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኮሜሳ ትብብር 1 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የተመደበ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የፈቃድና ቴክኒካል ሬሌሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ባህሩ ኦልጂራ በአወደ ጥናቱ መክፈቻ ስነ-ስትዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በቀጠናው ለሚገኙ ሀገራት ለኬኒያ፣ ሱዳንና ጂቡቲ የኤሌክትሪክ ሃይል በማቅረብ ላይ እንደምትገኝ ገልፀው በቀጣይም ለሌሎች የቀጠናው ሀገራት የሀይል አቅርቦት ትስስሩን ለማጠናከር በሂደት ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡
አቶ ባህሩ ጨምረውም እንደገለፁት ኢትዮጵያ ባላት ሰፊ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ ማዕከል ለመሆን እየሠራች ትገኛለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ውይይቱ የመጀመሪያው ቀን በዋነኝነት የኤሌክትሪክ ታሪፍ ወጥነት ኖሮት መቆጣጠር የሚያስችል ሞዴል ቀርቦ ጥናቱን ባጠናው አማካሪ ድርጅት ገለፃ ተደርጓል፡፡
የተሳታፊ ሀገራቱ ተወካዮችም ሞዴሉን በሀገራቱ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማጣጣም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ ዐውደ ጥናቱ ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት የሚጠናቀቅ ሲሆን በማህበሩ አባል ሀገራት ፕሮጀክቱን ለማስፈፀም የሚያስችሉ የተለያዩ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
 
  • Hits: 450

Contact Us

Petroleum and Energy Authority 

P.O.BOX 2554

Tel +251 

FAX +251

Email pea.info@pea.gov.et

Addis Ababa

Ethiopia

Address

Addis Ababa Kadco Group building #2 From 7th to 8th floor. Ethio china Friendship Avenue around Wello sefere.