በየትኛውም ደረጃ የሚሰሩ የኤሌክትሪክ ስራዎች ብቃታቸው በተረጋገጠ ሙያተኞች ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ።

 

በኤሌክትሪክ ስራ ሙያ ዘርፍ የብቃት ማረጋገጫ አስጣጥ ቅድመ ሁኔታና የፈተና አሰጣጥን የተመለከተ የሁለት ቀን የስልጠና ድጋፍ በሙያው ተሰማርተው ለሚገኙ ወጣቶች ተሰጠ።

የስልጠናው ዋና አላማ በተለያዩ ደረጃዎች የሚስሩ የኤሌክትሪክ ስራዎች የደህንነት ደረጃ ተጠብቆ እንዲስራ በዘርፉ የብቃት ማረጋገጫ ያላችው ሙያተኞችን ማበራከትና ወጣቶችን ማበረታታት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ አንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ለሰልጣኞች የንድፍ ሃሳብና የተግባር ልምምድ ስልጠና በባለሙያዎች ተሰጥቷል ።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ደህንነቱ የተረጋገጠ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲኖር ለማስቻል የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ሰራዎች ብቃት በሌላቸው ሰዎች እንዳይስሩ የሚደረግ የቁጥጥር ስራን ከማጠናከር ጎን ለጎን በዘርፉ ያሉ የህግ ማእቀፎችን ማስተዋወቅና ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው ለስልጣኞች በተሰጠ ገለፃ ወቅት ተመላክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በስልጠናው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች እንደገለፁት በህንፃዎች ግንባታ ወቅት ለኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ዲዛይን በቂ ትኩረት አለመኖርና ለኤሌክትሪክ ስራ በግብአትነት የሚውሉ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ደረጃቸውን ያልጠበቁ መሆን በስራቸው ላይ ተፅእኖ እንዳሳደረባቸው ገልፅዋል።

በባለስልጣን መ/ቤቱ በኩል በተሰጠ ምላሽ የህንፃዎች የኤሌክትሪክ መስመር ዲዛይን እና የተሰሩ የኤሌክትሪክ ሰራዎች ተፈተሽው ደህንነታቸው ሳይረጋገጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ማገናኘት በኢነርጂ ደንቡ ላይ የሚያስቀጣ ተግባር በመሆኑ መሰል ስራዎች ተሰርተው ሲገኙ እንደ ባለሙያ የአደጋ ተጋላጭነትን በተመለከት ለህብረተሰቡ ማስገንዘብ እንደሚገባ እና ለባለስልጣን መ/ቤቱ መጠቆም እንደሚቻል ተነግሯል።

በስልጠናው ማጠቃለያ ወጣቶቹ በሰጡት አስተያየት የብቃት ማረጋገጥ ሂደቱን የተመለከተ በቂ ግንዛቤ ማግኝታቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀው የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት አሰጣጡን በተመለከተ ምዘና ከመሰጠቱ በፊት ኦረንቴሽን ቢሰጥ እና የምዝገባ ሂደቱ በኦን ላየን የሚሰጥ መሆኑን ማስተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

 
  • Hits: 1171

Contact Us

Petroleum and Energy Authority 

P.O.BOX 2554

Tel +251 

FAX +251

Email pea.info@pea.gov.et

Addis Ababa

Ethiopia

Address

Addis Ababa Kadco Group building #2 From 7th to 8th floor. Ethio china Friendship Avenue around Wello sefere.