ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክትን አስመረቀች፡፡

 

ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክትን አስመረቀች፡፡

መስከረም 22/2018 (ነ.ኢ.ባ)

በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) መርቀው ያስጀመሩ ሲሆን በተመሳሳይም በዓመት 1.33 ቢሊዮን ሊትር ማምረት አቅም የሚኖረው ሁለተኛው ዙር ሥራም አስጀምረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ የጋዝ ማምረቻ ብቻ ሳይሆን ለማዳበሪያ ማምረቻ ወሳኝ የሆነ ግብዓት ማቅረቢያም ጭምር ሲሆን ይህ ደግሞ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም ለሃይል ማመንጫ እና ለክሪፕቶ ማይኒንግ ሥራዎች አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን የሚያቀርብ እንደሆነም ተነግሯል፡፡
 

Contact us

Petroleum and Energy Authority 

P.O.BOX 2554

Tel +251900115459

Email pea.info@pea.gov.et

Addis Ababa

Ethiopia

Address

Wollo Sefer
Cadco Business Group Building,
7th to 8th floor