ባለስልጣን መ/ቤቱ ብሔራዊ ኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂን ለመተግበር ከተሰጠው ኃላፊነት በመነሳት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ቀርፆ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል
|
ባለስልጣን መ/ቤቱ ብሔራዊ ኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂን ለመተግበር ከተሰጠው ኃላፊነት በመነሳት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ቀርፆ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ፕሮግራሞች አንዱ በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ላይ የሚተገበር የኢነርጂ አጠቃቀም ብቃትና ቁጠባ ኢነርጂ ኦዲት ፕሮግራም ነው፡፡ በዚህ ፕሮግራም ትገበራ የኢንደስትሪዎችን የኢነርጂ አጠቃቀም ብቃት ለማሻሻል የተለያዩ ስራዎች እየተሠሩ ሲሆን ከነዚህ መካከል ከከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚዎች ጋር የሚደረግ የፈቃደኝነት ኢነርጂ ማኔጅመንት ስምምነት ማደረግ፣በኢንደስትሪዎቹ ሊሚሠሩ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት እና ኢነርጂ ኦዲት ሥራዎችን ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በቀጣይም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን በዘርፉ የተጠኑ ጥናቶችን መሠረት በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የሚባክን ኢነርጂን ለማስቀረት የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመስራት ቅድመዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ |